የዐቢይ ጾም አምስተኛ እሑድ ደብረ ዘይት ተብሎ ይጠራል። ጌታችን ስለ ዳግም መምጣቱ ምልክትና ስለ ዓለም መጨረሻ የተናገረው በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በመሆኑ፥ ይህንን ዕለት ቅዱስ ያሬድ ደብረ ዘይት ብሎ ሰይሞታል።
በዕለቱም የቀረበው የቅዱስ ያሬድ ዝማሬ እንዲህ የሚል ነው…
“የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ የሰማይና የምድር ሠራዊት ሁሉ ይነቃነቃል። ያን ጊዜ በምድር የሚኖሩ ኃጢአተኞች ሁሉ ያለቅሳሉ። ጌታችንም ከአእላፍ መላእክት ጋር በትእዛዙና በቃሉ መሠረት ከሰማይ ወደ ምድር ይወርዳል። የእግዚአብሔር መለከትም ይሰማል። በዚያች ሰዓት እርሱ ያድነን። እርሱ የሕይወት ባለቤት ነውና።”
ይህንን ዝማሬ ቅዱስ ያሬድ የዘመረው… ማቴዎስ 24:3 ን ነው።
አዎን! ጌታችን በእርግጥ ዳግም ይመጣል።
በእርግጥም ዳግም፥ በድንገት፥ በግልጥና በክብር እኛን ለመውሰድ ይመጣል።
እንዴት ነው የምንጠብቀው???... ብላ ቤተክርሰቲያናችን ዋናውን ህይወታዊው ጥያቄ ታቀርብልናለች። መልሱንም…
ነቅተን... 1ተስ 5: 4-11
ልብሳችንን ለብሰን... ራእይ 16:15
መብራታችንን ይዘን... ማቴ 25:6
እንድንጠብቀው ትናንት አስተማረችን።
የተስፋችን ፍጻሜ ነውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ተግተን እንጠብቅ።
ስዓሊዎቹም... በተለያየ መልኩ እንዲህ ይሉናል…
Gustave Dore, Fineartnorthamerica.com
Orthodox Christian Church Icon
Hans Memling, 1466-1473.
National Museum, Gdańsk
Michelangelo, 1536-1541
Sistine Chapel ceiling
William Blake ,1808, Ink and
watercolour
አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና
ራእይ 22:20
He who testifies to these things
says, “Surely I am coming soon.” Amen. Come, Lord Jesus!
Revelation
22:20
No comments:
Post a Comment